ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ ስብሰባቸውን አቋርጠው ሐዋሳ ገቡ!



ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ እና አቶ አብርሀም ማርሻሎ የብልፅግና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባን አቋርጠው ነው ሐዋሳ የገቡት።

ሁለቱ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ሐዋሳ የገቡት በዩኒቨርስቲ በተማሪዎች ላይ የደረሰውን አደጋ እንደሰሙ መሆኑን ታውቋል።

ርዕሰ መስተዳደሩ እና የብልፅግና ፓርቲ ሀላፊው በተፈጠረው አደጋ የተጎዱ ተማሪዎችን ለማየት ሆስፒታል ቦታው ድረስ በመሄድ መመልከት እና ማፅናናት ችለዋል።
/ሐዋሳ ከተማ ሕዝብ ግንኙነት/

Published by 𝗬𝗮𝘀𝗶𝗻 𝗘𝗻𝗱𝗿𝗶𝘀

Bloger

Leave a comment

Design a site like this with WordPress.com
Get started