ፍልቃቂ—እውነት

በጭቡ ዘመን ላይ ፥ በተድበሰበሰ
ቀናት ተሰፍሮለት … እድሜ ላጋበሰ
ውሸት ተረፍቆ… የህሊናው ምስል ካልተበሳበሰ
ጉድና ጅራቱ… ልክ እንደ ባቢሎን ተክቦ
… ተክቦ…
በቂም በጥላቻ… ቀናው ተወስቦ
ጭብጨባና ዲስኩር… ሀቁን ሲያንጋልለው
ነፃ አውጪህ ባዩ ነው ግንባርክን የሚለው
___________///////___________
/አብርሃም ተክሉ/

Published by 𝗬𝗮𝘀𝗶𝗻 𝗘𝗻𝗱𝗿𝗶𝘀

Bloger

Leave a comment

Design a site like this with WordPress.com
Get started